2025–2026 Academic Yearየ2017 የትምህርት ዓመትالعام الدراسي 2025–2026

Parent Handbookየወላጅ መመሪያدليل الأهالي

Practical guidelines, policies, and expectations for Abadir School families.ለአባዲር ትምህርት ቤት ቤተሰቦች ጠቃሚ መመሪያዎች፣ ፖሊሲዎች እና የሚጠበቁ ነገሮች።إرشادات عملية وسياسات وتوقعات لعائلات مدرسة أبادير.

English Handbookየእንግሊዝኛ መመሪያالدليل الإنجليزي

Download the full parent handbook in English.ሙሉውን የወላጅ መመሪያ በእንግሊዝኛ ያውርዱ።قم بتنزيل دليل الأهالي الكامل بالإنجليزية.

Download PDFPDF ያውርዱتنزيل PDF

Amharic Handbookየአማርኛ መመሪያالدليل الأمهرية

Download the full parent handbook in Amharic.ሙሉውን የወላጅ መመሪያ በአማርኛ ያውርዱ።قم بتنزيل دليل الأهالي الكامل بالأمهرية.

Download PDFPDF ያውርዱتنزيل PDF
Welcomeመግቢያترحيب

Message from the Head of Schoolከመምህራን ርዕሰ መምህር የተላከ መልዕክትرسالة من مدير المدرسة

Dear Abadir School Families,ለአባዲር ትምህርት ቤት ክቡራን ወላጆችና አሳዳጊዎች፣عائلات مدرسة أبادير المحترمة،

Welcome to the 2025-2026 academic year! Whether you're returning or new, we're thrilled to have you as part of our community. This year, we are committed to making Abadir great again through necessary reforms. Our focus remains on providing a holistic educational experience that nurtures intellectual curiosity, fosters creativity, and instills strong ethical values, all while celebrating our rich heritage.የ2017 የትምህርት ዘመን እንኳን አደረሳችሁ! ነባርም ሆኑ አዲስ ተማሪዎቻችን፣ በማህበረሰባችን ውስጥ በመገኘታችሁ የተሰማንን ደስታ እንገልፃለን። በዚህ የትምህርት ዘመን፣ አባዲርን ወደ ቀድሞ ስመ-ገናናነቱ ለመመለስ የሚያስችሉ አስፈላጊ ማሻሻያዎችን ተግባራዊ ለማድረግ ቆርጠን ተነስተናል። ዋና ትኩረታችን ሁለንተናዊ ትምህርትን በማቅረብ ላይ ሲሆን፣ ይህም የማወቅ ፍላጎትን የሚያነሳሳ፣ የፈጠራ ችሎታን የሚያጎለብት፣ እና ጠንካራ ሥነ-ምግባርን የሚያንጽ ሆኖ የከበረውን ቅርሳችንን ያላበሰ ነው።أهلاً وسهلاً بكم في العام الدراسي 2025–2026! سواء كنتم من العائلات العائدة أو الجديدة، نحن سعداء بانضمامكم إلى مجتمعنا. نلتزم هذا العام بإعادة أبادير إلى سابق عهدها من خلال إصلاحات ضرورية، مع التركيز على تقديم تعليم شامل يعزز الفضول الفكري والإبداع والقيم الأخلاقية القوية.

This Parent Booklet is your essential guide to Abadir School life. It details our core values, academic programs, policies, and expectations for students, parents, and staff. We've aligned our practices with the Ethiopian Education Policy to ensure a relevant and robust education for your child.ይህ የወላጆች የእጅ መጽሐፍ ስለ አባዲር ትምህርት ቤት ማወቅ የሚገባችሁን ሁሉ የያዘ ቁልፍ መመሪያችሁ ነው። የመመሪያ እሴቶቻችንን፣ የትምህርት ፕሮግራሞችን፣ ደንቦችን እንዲሁም ከተማሪዎች፣ ከወላጆች እና ከሠራተኞች የሚጠበቁ ነገሮችን በዝርዝር ያትታል። ለልጆቻችሁ ጥራት ያለውና አግባብነት ያለው ትምህርት እንዲደርሳቸው ለማድረግ የአሰራር ሂደቶቻችንን ከሀገራችን የትምህርት ፖሊሲ ጋር አጣጥመናል።يعد هذا الدليل الإرشادي الأساسي لحياة مدرسة أبادير. يوضح قيمنا الأساسية وبرامجنا الأكاديمية وسياساتنا وتوقعاتنا من الطلاب والأهالي والموظفين، وتماشينا مع سياسة التعليم الإثيوبية لضمان تعليم قوي وملائم لطفلكم.

Sincerely, Timaj Abubakar, General Manager, Mekanisa Abadir Mosque Schoolከአክብሮት ጋር፣ ቲማጅ አቡበከር፣ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የመካኒሳ አባዲር መስጅድ ት/ቤትمع التقدير، تيماج أبوبكر، المدير العام، مدرسة مسجد مكانيسا أبادير

Our Foundationየእኛ መሰረትأساسنا

Mission, Vision & Core Valuesተልዕኮ፣ ራዕይ እና መሠረታዊ እሴቶችالمهمة والرؤية والقيم الأساسية

Our Missionተልዕኳችንمهمتنا

Empowering Students for Lifeተማሪዎችን ለህይወት ማብቃትتمكين الطلاب للحياة

To empower students through a dynamic and inclusive learning environment, fostering academic excellence and deep ethical values, so they become competitive, compassionate individuals of high moral character.ተማሪዎችን በተለዋዋጭ እና አካታች የትምህርት አካባቢ ለማበረታታት፣ አካዳሚያዊ ልቀትን እና ጥልቅ የስነ-ምግባር እሴቶችን በማጎልበት፣ በዚህም ተወዳዳሪ፣ ሩህሩህ እና የሞራል ባህሪ ያላቸው ግለሰቦች ይሆናሉ።تمكين الطلاب من خلال بيئة تعليمية ديناميكية وشاملة، وتعزيز التميز الأكاديمي والقيم الأخلاقية العميقة، حتى يصبحوا أفرادًا تنافسيين ورحيمين يتمتعون بأخلاق عالية.

Our Visionራዕያችንرؤيتنا

Ethiopia's Premier Schoolየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ትምህርት ቤትالمدرسة الرائدة في إثيوبيا

To be Ethiopia's premier school, renowned for its holistic and nurturing environment that cultivates academic distinction and moral fortitude. We aspire to develop well-rounded, socially competent problem-solvers who are mature citizens committed to lifelong learning and contributing positively to society.የአካዳሚክ ልዩነትን እና የሞራል ጥንካሬን የሚያጎለብት ሁለንተናዊ እና ተንከባካቢ አካባቢዋ የታወቀ የኢትዮጵያ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመሆን።أن نكون المدرسة الرائدة في إثيوبيا، معروفين ببيئتنا الشاملة والراعية التي تنمي التميز الأكاديمي والثبات الأخلاقي. نطمح إلى تطوير مواطنين ناضجين، قادرين على حل المشكلات، ملتزمين بالتعلم مدى الحياة والمساهمة إيجابيًا في المجتمع.

Our Core Valuesመሠረታዊ እሴቶቻችንقيمنا الأساسية

Excellenceልቀትالتميز
Responsibilityኃላፊነትالمسؤولية
Respectአክብሮትالاحترام
Integrityታማኝነትالنزاهة
Communityማኅበረሰብالمجتمع
Resilienceጽናትالصمود

The 4 Cs of Abadirየአባዲር "አራቱ መ"الأربعة مبادئ أبادير

Care — kindness and empathy for ourselves and others. Courage — doing the right thing and learning from mistakes. Curiosity — approaching the world with an open, inquiring mind. Commitment — dedicating ourselves to studies, responsibilities, and daily improvement.መተሳሰብ — ለራሳችን፣ ለጓደኞቻችንና ለምንኖርበት ዓለም ከልብ ማሰብና መራራት። መደፈር — ስህተት ስንሠራ ለማመን፣ ትክክል የሆነውን ለማድረግና ሐሳባችንን በድፍረት ለመናገር። መመራመር — ትምህርትንና ዓለምን በክፍትና በጠያቂ አዕምሮ መቅረብ። መጽናት — ለትምህርታችን፣ ለኃላፊነቶቻችንና በየዕለቱ ራስን ለማሻሻል ቁርጠኛ መሆን።الاهتمام — اللطف والتعاطف مع أنفسنا والآخرين. الشجاعة — فعل الصواب والتعلم من الأخطاء. الفضول — مواجهة العالم بعقل مفتوح واستقصائي. الالتزام — التفاني في الدراسة والمسؤوليات والتحسن اليومي.

General School Informationማወቅ የሚገባዎ ጠቅላላ መረጃمعلومات المدرسة العامة

Contact, Hours & Calendarአድራሻ፣ ሰዓት እና የትምህርት መርሃ ግብርالاتصال والساعات والتقويم

General Enquiriesለአጠቃላይ ጥያቄዎችالاستفسارات العامة

+251 11 320 2134

School Hoursየትምህርት ሰዓትساعات المدرسة

Gates open 7:30 AM; morning assembly 7:50 AM; classes 8:30 AM – 3:10 PM; extra help 3:10 PM – 3:55 PM; gates close at 5:00 PM.ደጎች ከጠዋቱ 1:30 ይከፈታሉ፣ የጠዋት ሰልፍ ከ1:50 ይጀምራል፣ ትምህርት ከ2:30 እስከ 9:10፣ ተጨማሪ የማጠናከሪያ ከ9:10 እስከ 9:55፣ ደጎች ከ11:00 ይዘጋሉ።تفتح الأبواب في 7:30 صباحًا، التجمع الصباحي 7:50، الحصص 8:30 صباحًا – 3:10 عصرًا، الدعم الإضافي 3:10 – 3:55، تغلق الأبواب في 5:00 مساءً.

📅

Saturday Tutorialsየቅዳሜ ትሁት ፕሮግራምالدروس التكميلية يوم السبت

Mandatory for Grades 6, 8, and 12 every Saturday, 8:15 AM – 12:15 PM. Other students may attend by arrangement.ለ6፣ 8 እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ግዴታ ነው፤ ዘወትር ቅዳሜ ከጠዋቱ 2:15 እስከ 6:15። ሌሎች ተማሪዎችም በውይይት እንድሰጥ ይደረጋል።إلزامية للصفوف 6 و8 و12 كل سبت من 8:15 صباحًا حتى 12:15 ظهرًا. يمكن للطلاب الآخرين الحضور بالتنسيق.

Daily Scheduleየዕለት ፕሮግራምالجدول اليومي

TimeሰዓትالوقتActivityድርጊትالنشاط
7:30 AM1:307:30 صGates openደጎች ይከፈታሉتفتح الأبواب
7:50 AM1:507:50 صMorning line-upየጠዋት ሰልፍالصف الصباحي
8:00 – 8:15 AM2:00 – 2:158:00 – 8:15 صFlag Ceremonyየሰንደቅ ዓላማ ሥነ ሥርዓትمراسم رفع العلم
8:15 – 8:25 AM2:15 – 2:258:15 – 8:25 صHomeroom attendanceየስም መጥሪያحضور الفصل
8:30 AM – 12:35 PM2:30 – 6:358:30 ص – 12:35 مMorning classesየጠዋት ትምህርትحصص الصباح
10:00 – 10:20 AM4:00 – 4:2010:00 – 10:20 صSnack breakየቁርስ እረፍትاستراحة الوجبة الخفيفة
12:30 – 1:30 PM6:30 – 7:3012:30 – 1:30 مLunchየምሳ ሰዓትالغداء
1:35 – 1:40 PM7:35 – 7:401:35 – 1:40 مAfternoon attendanceየከሰዓት በኋላ ሰልፍحضور العصر
1:40 – 3:10 PM7:40 – 9:101:40 – 3:10 مAfternoon classesየከሰዓት በኋላ ትምህርትحصص العصر
3:10 – 3:55 PM9:10 – 9:553:10 – 3:55 مTutorial / extra helpየማጠናከሪያ ትምህርትدروس تقوية
4:00 PM10:004:00 مSchool day endsየዕለቱ ትምህርት ይጠናቀቃልانتهاء اليوم الدراسي
5:00 PM11:005:00 مGates closeደጎች ይዘጋሉإغلاق الأبواب

Key Academic Datesየ2018 ዓ.ም የትምህርት መርሃ ግብርتواريخ أكاديمية رئيسية

DateቀንالتاريخActivityተግባርالنشاط
Jul 8 – Aug 29, 2025ሐምሌ 1 – ነሐሴ 23, 20178 يوليو – 29 أغسطس 2025Registrationምዝገባالتسجيل
Sep 2, 2025ነሐሴ 27, 20172 سبتمبر 2025School regulations briefingስለ ደንቦች ገለጻإيجاز اللوائح
Sep 15, 2025 – Jan 30, 2026መስከረም 5 – ጥር 22, 201815 سبتمبر 2025 – 30 يناير 2026First Semesterየመጀመሪያ ሴምስተርالفصل الأول
Feb 9 – Jun 25, 2026የካቲት 2 – ሰኔ 18, 20189 فبراير – 25 يونيو 2026Second Semesterሁለተኛ ሴምስተርالفصل الثاني
Feb 15, 2026የካቲት 7, 201815 فبراير 2026Parent-Teacher Conferencesየወላጅ-መምህራን ስብሰባاجتماعات أولياء الأمور
Nov 24–26, 2025ህዳር 15–17, 201824–26 نوفمبر 2025Mid-term assessments (Term 1)የመጀመርያው ወሰነ-ትምህርት አጋማሽ ምዘናالتقييمات النصفية (الفصل 1)
Jan 26–30, 2026ጥር 17–22, 201826–30 يناير 2026End-of-term exams (Term 1)የ1ኛ ሴምስተር ማጠቃለያ ፈተናامتحانات نهاية الفصل الأول
Apr 19–21, 2026ሚያዝያ 11–13, 201819–21 أبريل 2026Mid-term assessments (Term 2)የሁለተኛው ወሰነ-ትምህርት አጋማሽ ምዘናالتقييمات النصفية (الفصل 2)
May 31 – Jun 4, 2026ግንቦት 23 – 27, 201831 مايو – 4 يونيو 2026Grade 6 & 8 Model Examየ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ሞዴል ፈተናاختبار نموذجي للصفوف 6 و8
May 31 – Jun 4, 2026ግንቦት 23 – 27, 201831 مايو – 4 يونيو 2026Grade 12 Model Exam (online)የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና (በኢንተርኔት)اختبار نموذجي للصف 12 (إلكتروني)
Jun 7 – 18, 2026ግንቦት 30 – ሰኔ 11, 20187–18 يونيو 2026Grade 6 & 8 Ministry Examየሚኒስትሪ ፈተና (ለ6ኛ እና 8ኛ ክፍል)امتحان الوزارة للصفوف 6 و8
Jun 21 – 25, 2026ሰኔ 14 – 18, 201821–25 يونيو 2026End-of-term exams (Term 2)የ2ኛ ሴምስተር ማጠቃለያ ፈተናامتحانات نهاية الفصل الثاني
Jul 6, 2026ሰኔ 30, 20186 يوليو 2026Report cards & end of school yearየውጤት መግለጫ እና የዓመቱ መዝጊያبطاقات التقارير ونهاية العام

School Profile & Historyታሪካችንና ማንነታችንتاريخ المدرسة وملفها

Abadir School, located in the Ledeta Subcity of Addis Ababa, has proudly served its community since its establishment in 1994 G.C. We began with 191 students in Kindergarten and First Cycle Elementary, supported by 9 staff members. Within a few years, we expanded to Second Cycle Primary education. By 2002 G.C., Abadir School offered General Secondary Education, and five years later, Preparatory Education.የአባዲር ትምህርት ቤት በአዲስ አበባ በልደታ ክፍለ ከተማ የሚገኝ ሲሆን ከ1994 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ማህበረሰቡን በኩራት አገልግሏል። በመዋዕለ ሕጻናት እና በአንደኛ ደረጃ የመጀመሪያ ሳይክል 191 ተማሪዎችን እና 9 ሰራተኞችን በመያዝ ጀመረ። በጥቂት ዓመታት ውስጥ የሁለተኛ ደረጃ የመጀመሪያ ሳይክል ትምህርትን አስፋፋ። በ2002 እ.ኤ.አ. የጠቅላላ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መስጠት ጀመረ፤ ከአምስት ዓመታት በኋላ ደግሞ የመሰናዶ ትምህርት አስጀመረ።تقع مدرسة أبادير في مدينة ليديتا في أديس أبابا، وقد خدمت مجتمعها بفخر منذ تأسيسها عام 1994. بدأت بـ 191 طالبًا في رياض الأطفال والحلقة الأولى الابتدائية، بدعم من 9 موظفين. في غضون سنوات قليلة، توسعت لتشمل الحلقة الثانية الابتدائية. بحلول عام 2002، بدأت بتقديم التعليم الثانوي العام، وبعد خمس سنوات أضافت التعليم التحضيري.

Today, Abadir School is a thriving educational institution with over 1,200 students and 130 committed staff. We are fully accredited by the Addis Ababa Education Bureau. One hundred percent of our graduates are college-bound, pursuing higher education at universities worldwide. We follow the Ethiopian standard-based curriculum from Kindergarten through Grade 12.በአሁኑ ወቅት አባዲር ትምህርት ቤት ከ1200 በላይ ተማሪዎች እና 130 ቁርጠኛ ሠራተኞች ያሉት ታላቅ የትምህርት ተቋም ሆኗል። በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ሙሉ ዕውቅና ተሰጥቶታል። ሁሉም ተመራቂዎቻችን በዓለም ዙሪያ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ናቸው። ከመዋዕለ ሕጻናት እስከ 12ኛ ክፍል የኢትዮጵያን ደረጃ-ተኮር ሥርዓተ ትምህርት እንከተላለን።اليوم، أصبحت مدرسة أبادير مؤسسة تعليمية مزدهرة تضم أكثر من 1200 طالب و130 موظفًا ملتزمًا. نحن معتمدون بالكامل من مكتب التعليم في أديس أبابا. مائة بالمائة من خريجينا يلتحقون بالجامعات في جميع أنحاء العالم. نتبع المنهج الإثيوبي المعتمد من رياض الأطفال حتى الصف الثاني عشر.

Student Servicesየተማሪዎች አገልግሎትخدمات الطلاب

Supplies, Transport, Records & Libraryቁሳቁሶች፣ ትራንስፖርት፣ ሰነዶች እና ላይብረሪالمستلزمات والنقل والسجلات والمكتبة

01

Textbooks & Suppliesመማሪያ መጻሕፍት እና የትምህርት ቁሳቁሶችالكتب والمستلزمات

Parents purchase textbooks according to the list provided by the school at the beginning of the year. Each grade receives a supplies list (notebooks, pens, pencils, art materials). All students need a pencil case with pencils, sharpener, pen, eraser, and ruler. Years 5+ also need a calculator and drawing compass for occasional lessons.ወላጆች በትምህርት ዘመኑ መጀመሪያ ላይ በትምህርት ቤቱ በሚሰጠው ዝርዝር መሠረት የራሳቸውን መማሪያ መጻሕፍት ይገዛሉ። ለእያንዳንዱ ክፍል የሚፈለጉ የትምህርት ቁሳቁሶች (ደብተሮች፣ እስክሪብቶዎች፣ እርሳሶች፣ የሥነ-ጥበብ መገልገያዎች) ይሰጣሉ። ሁሉም ተማሪዎች እርሳስ፣ መቅረጫ፣ ብዕር፣ ላጲስና ማስመሪያ የያዘ የእርሳስ ማስቀመጫ ያስፈልጋቸዋል። ለ5ኛ ክፍልና ከዚያ በላይ አልፎ አልፎ ካልኩሌተር እና የጂኦሜትሪ ኮምፓስ ያስፈልጋል።تشتري الأهالي الكتب الدراسية وفقًا للقائمة التي تقدمها المدرسة في بداية العام. يتلقى كل صف قائمة بالمستلزمات (دفاتر، أقلام، مواد فنية). يحتاج جميع الطلاب إلى مقلمة بها أقلام ومبراة وقلم ومسطرة. يحتاج طلاب الصف الخامس فأعلى إلى آلة حاسبة وبوصلة رسوم.

02

Transportationየትራንስፖርት አገልግሎትالنقل

Abadir School does not operate its own school bus service. Parents/guardians are responsible for arranging their child's transportation to and from school.የትራንስፖርት አገልግሎት እንደማንሰጥ በትህትና እየገለጽን፣ ወላጆች የልጆቻቸውን የጉዞ ሁኔታ በራሳቸው እንዲያመቻቹ እንጠይቃለን።لا تدير مدرسة أبادير حافلة مدرسية خاصة. يتحمل الأهالي مسؤولية تنظيم نقل أطفالهم من وإلى المدرسة.

03

After-School Programከመደበኛ ትምህርት ሰዓት ውጪ ፕሮግራምالبرنامج ما بعد المدرسة

A supervised After-School Program provides a safe and enriching environment after regular hours, including homework time, recreational activities, arts and crafts, and various clubs. Details on schedules, activities, fees, and registration are communicated each term.አባዲር ትምህርት ቤት ከመደበኛው የትምህርት ሰዓት በኋላ ደኅንነቱ የተጠበቀና ክህሎትን የሚያዳብር ፕሮግራም ያቀርባል። ይህ ፕሮግራም የቤት ሥራ ጊዜን፣ የመዝናኛ እንቅስቃሴዎችን፣ የሥነ-ጥበብና የእጅ ሥራዎችን እንዲሁም የተለያዩ ክበባትን ያካትታል። ስለ ፕሮግራሙ የጊዜ ሰሌዳ፣ እንቅስቃሴዎች፣ ክፍያና ምዝገባ ዝርዝር መረጃ በእያንዳንዱ ሴሚስተር ይገለጻል።يوفر البرنامج الإشرافي ما بعد المدرسة بيئة آمنة وغنية بعد ساعات الدراسة، ويشمل وقت الواجبات المنزلية والأنشطة الترفيهية والفنون والحرف والنوادي المختلفة. تُعلن التفاصيل الخاصة بالجدول والأنشطة والرسوم والتسجيل كل فصل.

04

Student Recordsየተማሪዎች ሰነድ አያያዝسجلات الطلاب

During registration, parents must provide: a discipline clearance from administration, a report card showing promotion/pass, confirmation of cleared previous year's tuition, one month's tuition plus registration fee, birth certificate copy, Fayda ID copy, completed registration form, and a signed acknowledgment of the school handbook.ምዝገባ ወቅት፣ የሚከተሉትን ማሟላት ያስፈልጋል፦ ከአስተዳደር ክፍል የተሰጠ የሥነ-ምግባር ማረጋገጫ፣ ማለፉን የሚያሳይ የውጤት መግለጫ፣ ያለፈው ዓመት የትምህርት ክፍያ ዕዳ ሙሉ በሙሉ የተከፈለ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማረጋገጫ፣ የአንድ ወር የትምህርት ክፍያ እና የምዝገባ ክፍያ፣ የልደት የምስክር ወረቀት ቅጂ፣ የፈይዳ መታወቂያ ቅጂ፣ በትክክል የተሞላ የምዝገባ ቅጽ እና የትምህርት ቤቱን ደንቦች/መመሪያ መጽሐፍ አንብቦ ለመቀበል የተፈረመ ስምምነት።أثناء التسجيل، يجب على الأهالي تقديم: تصريح انضباط من الإدارة، بطاقة تقارير تبين النجاح، تأكيد تسوية الرسوم الدراسية للعام السابق، رسوم شهر دراسي واحد بالإضافة إلى رسوم التسجيل، نسخة من شهادة الميلاد، نسخة من بطاقة فايدا، استمارة تسجيل مكتملة، وإقرار موقع باستلام دليل المدرسة.

05

Lost & Foundየጠፋና የተገኘ ዕቃالمفقودات

Lost items should be reported to the school office. We encourage parents to label all personal belongings, especially uniforms and stationery, to help return lost items to their owners.የጠፉ ዕቃዎች ወደ ትምህርት ቤቱ ጽ/ቤት መዘገብ አለባቸው። በተለይ የደንብ ልብስ እና የጽህፈት ቁሳቁሶች ላይ የልጅዎን ስም በማጻፍ ጠፋ ዕቃዎች ለባለቤታቸው እንዲመለሱ ይተባበሩ።يجب الإبلاغ عن الأغراض المفقودة لمكتب المدرسة. نشجع الأهالي على وضع اسم الطفل على جميع الأمتعة الشخصية، خاصة الزي المدرسي والقرطاسية، لإعادة الأغراض المفقودة لأصحابها.

06

Library Policyየላይብረሪ መጻሕፍት ደንብسياسة المكتبة

Students can borrow books weekly: one book for Years 1–2, two books for Years 3 and above. All books are due weekly; failure to return within 14 days suspends borrowing privileges until overdue books are returned. Students must protect books using a strong folder. A 700 Birr replacement fee applies to lost or irreparably damaged books. Books may be renewed for one additional week.ተማሪዎች በየሳምንቱ መጻሕፍትን መዋስ ይችላሉ፦ ከ1ኛ እስከ 2ኛ ክፍል አንድ መጽሐፍ፣ ከ3ኛ ክፍልና ከዚያ በላይ ሁለት መጻሕፍት። ሁሉም መጻሕፍት በየሳምንቱ መመለስ አለባቸው። አንድ መጽሐፍ በ14 ቀናት ውስጥ ካልተመለሰ፣ ሁሉም የቆዩ መጻሕፍት እስኪመለሱ ድረስ መዋስ ይከለከላል። ተማሪዎች መጻሕፍትን በጠንካራ ፎልደር መጠበቅ አለባቸው። ለጠፋ ወይም ሊጠገን በማይችል ሁኔታ ለተበላሸ መጽሐፍ 700 ብር የመተኪያ ክፍያ ይኖራል። መጻሕፍትን ለአንድ ተጨማሪ ሳምንት ማሳደስ ይቻላል።يمكن للطلاب استعارة الكتب أسبوعيًا: كتاب واحد للصفوف 1–2، وكتابان للصف الثالث فأعلى. تُعاد جميع الكتب أسبوعيًا؛ عدم الإرجاع خلال 14 يومًا يعلق امتياز الاستعارة حتى إعادة الكتب المتأخرة. يجب حماية الكتب باستخدام مجلد قوي. تطبق رسوم استبدال 700 بير على الكتب المفقودة أو التالفة بشكل لا يمكن إصلاحه. يمكن تجديد الكتب لأسبوع إضافي.

Student Life & Well-beingየተማሪዎች ሕይወት እና ደህንነትحياة الطلاب ورفاهيتهم

Character, Behavior & Daily Expectationsባህሪ፣ ሥነ-ምግባር እና የዕለት ተዕለት የሚጠበቁ ነገሮችالشخصية والسلوك والتوقعات اليومية

Cultivating Character & Positive Behaviorመልካም ሥነ-ምግባርን በጋራ መገንባትتنمية الشخصية والسلوك الإيجابي

At Abadir School, we believe in nurturing not just minds, but character. Our approach is proactive, focusing on developing well-rounded individuals who contribute positively to our community. We build strong relationships with students based on love, respect, and understanding, guiding them to make choices that serve their best interests and those of others.በአባዲር ትምህርት ቤት እምነታችን፣ ትምህርት ማለት አዕምሮን ከማጎልመስ ባለፈ መልካም ሰብዕናን መገንባት ነው። የሥነ-ምግባር መርኃችን ልጆቻችን ለማኅበረሰቡ በጎ የሚያደርጉ፣ አዛኝና ኃላፊነት የሚሰማቸው ዜጎች እንዲሆኑ አስቀድሞ በማዘጋጀት ላይ ያተኩራል። ይህንንም የምናደርገው በፍቅር፣ በመከባበርና በመተሳሰብ ላይ የተመሠረተ ጠንካሮ ግንኙነት በመፍጠር ነው።في مدرسة أبادير، نؤمن بتنمية العقل والشخصية معًا. نهجنا استباقي، يركز على تطوير أفراد متكاملين يساهمون بإيجابية في مجتمعنا. نبني علاقات قوية مع الطلاب قائمة على الحب والاحترام والتفاهم، ونوجههم لاتخاذ قرارات تخدم مصالحهم ومصالح الآخرين.

We celebrate good choices through daily Kudos Corners, weekly positive notes home, and monthly Abadir Achievers recognition. Homeroom teachers act as champions for their groups, fostering a strong "Abadir Family" bond.በጎ ምርጫዎችን በየክፍሉ በሚገኘው የምስጋና ማዕዘን፣ በየሳምንቱ በቤተሰብ የሚላክ መልእክት እና በየወሩ የአባዲር የልህቀት ተሸላሚዎች ማወደስ እንቀጥላለን። የክፍል መምህራን ለተመደበላቸው ቡድን ልዩ ድጋፍ ያደርጋሉ፤ ይህም ጠንካሩን "የአባዲር ቤተሰብ" ትስስር ያጎለብታል።نحتفي بالاختيارات الجيدة من خلال زوايا التقدير اليومية، والملاحظات الإيجابية الأسبوعية للمنزل، وتكريم "أبادير للإنجاز" الشهري. يعمل مدرسو الفصول كداعمين لمجموعاتهم، مما يعزز رابط "عائلة أبادير" القوي.

Behavior Policy: Levels of Interventionየሥነ-ምግባር እርምት አሰጣጥና የአያያዝ ሥርዓትسياسة السلوك: مستويات التدخل

Our behavior model is Abadir C.A.R.E.S. We address poor choices as opportunities for growth and learning, prioritizing restoration of relationships and minimizing disruption. Specific staff use discretion to apply guidelines fairly. All disciplinary actions are recorded in the student's file.የምንመራበት የሥነ-ምግባር ሞዴል "አባዲር C.A.R.E.S." ይሰኛል። ለማስተካከል የሚያደረገው እርምጃ እንደ ዕድገት እና የመማሪያ መንገድ እንቆጥራቸዋለን። የተሳሳቱ ምርጫዎች እንደ ክብደታቸው በአራት ደረጃዎች የተከፈሉ ሲሆን፣ የተለያዩ የጣልቃ ገብነት እርምጃዎችን ይጠይቃሉ። ሁሉም የሥነ-ምግባር እርምጃዎች በተማሪው የግል ፋይል ውስጥ ይመዘገባሉ።نموذج السلوك لدينا هو C.A.R.E.S. أبادير. نتعامل مع الاختيارات السيئة كفرص للنمو والتعلم، مع إعطاء الأولوية لإصلاح العلاقات وتقليل الإزعاج. يطبق الموظفون المحددون هذه الإرشادات بعدالة. يتم تسجيل جميع الإجراءات التأديبية في ملف الطالب.

Level 1 — Classroom & Teacher Guidedደረጃ 1 — በክፍል ደረጃ እና በአስተማሪ የሚመሩالمستوى 1 — إرشاد الفصل والمعلم

Less serious issues managed by the subject or homeroom teacher. Examples: repeated disruption, being out of class without permission, teasing, chewing gum, littering. Consequences: warnings, notes home, time-out, reflection sheets.ቀላል ጉዳዮች በትምህርት መምህር ወይም በክፍል ጠባቂ የሚታዩና የሚስተካከሉ። ምሳሌዎች፦ በተደጋጋሙ የክፍል ሥርዓት ማወክ፣ ያለፈቃድ ከክፍል ውጪ መገኘት፣ ሌሎችን ማሾፍ፣ ማስቲካ ማኘክ/ከረሜላ መብላት፣ ቆሻሻ መጣል። የሚወሰዱ እርምጃዎች፦ ማስጠንቀቂያ፣ ለቤተሰብ የሚላክ ማስታወሻ፣ ከቡድን ለብቻ ማቆየት (ታይም-አውት)፣ ራስን የመገምገሚያ ወረቀት መሙላት።مشكلات أقل خطورة يديرها معلم المادة أو معلم الفصل. أمثلة: الإزعاج المتكرر، الخروج من الفصل بدون إذن، التنمر، مضغ العلكة، رمي القمامة. العواقب: التحذيرات، الملاحظات المنزلية، الوقت المنفصل، أوراق التأمل.

Level 2 — Parental Contact & Classroom Consequencesደረጃ 2 — የወላጅ ተሳትፎን የሚጠይቁ ጉዳዮችالمستوى 2 — التواصل مع الأهل وعواقب الفصل

More serious issues or repeated Level 1 infractions requiring intervention beyond the classroom teacher. Examples: repeated Level 1 offenses, cheating, disrespect to adults, spreading rumors, inappropriate physical contact, throwing objects. Consequences: parental contact and classroom-level consequence.ይበልጥ ከበድ ያሉ ወይም ተደጋጋሚ የደረጃ 1 ጥፋቶች። ምሳሌዎች፦ የደረጃ 1 ጥፋቶችን መድገም፣ በፈተና መኮረጅ፣ ንብረት ማበላሸት፣ ለታላላቆች አክብሮት መንፈግ፣ ሐሜት ማሰራጨት/ጉልበተኝነት፣ ተገቢ ያልሆነ አካላዊ ንክኪ። የሚወሰዱ እርምጃዎች፦ ከወላጅ ጋር ግንኙነት (በሪፖርት፣ በስልክ ወይም በውይይት) እና በአስተማሪው የሚወሰን የክፍል ውስጥ የማስተካከያ እርምጃ።مشكلات أكثر خطورة أو انتهاكات متكررة للمستوى 1 تتطلب تدخلًا أبعد من معلم الفصل. أمثلة: تكرار مخالفات المستوى 1، الغش، عدم احترام الكبار، نشر الشائعات، لمس جسدي غير لائق، رمي الأشياء. العواقب: التواصل مع الأهل وعقوبة على مستوى الفصل.

Level 3 — Administrative Interventionደረጃ 3 — በአስተዳደር ደረጃ የሚታዩ ከባድ ጥፋቶችالمستوى 3 — التدخل الإداري

Severe breaches or persistent Level 2 infractions threatening safety or the learning environment. Examples: repeated Level 2 offenses, obscene language, fighting, dangerous objects, intentional property damage, skipping school. Consequences: parent-student meeting with administration, behavior contract, detention, or suspension.የትምህርት ቤቱን የሥነ-ምግባር ደንብ በእጅጉ የሚጥሱ ወይም የማኅበረሰቡን ደኅንነት፣ ሰላምና የመማሪያ ምኅዳርን የሚፈታተኑ ተደጋጋሚ የደረጃ 2 ጥፋቶች። ምሳሌዎች፦ የደረጃ 2 ጥፋቶችን መድገም፣ ጸያፍ ቋንቋ መጠቀም፣ መደባደብ ወይም ጉዳት ለማድረስ መሞከር፣ አደገኛ ዕቃዎችን ይዞ መምጣት፣ ሆን ብሎ ንብረት ማውደም፤ ከትምህርት ቤት/ከክፍል መቀረት። የሚወሰዱ እርምጃዎች፦ ከትምህርት ቤቱ አስተዳደር ጋር የወላጅ-ተማሪ ስብሰባ፤ ይህም ወደ ሥነ-ምግባር ውል፣ ከትምህርት በኋላ እንዲቆዩ ማድረግ (ዲቴንሽን) ወይም ከትምህርት ገበታ ማገድ (suspension) ሊያመራ ይችላል።انتهاكات خطيرة أو متكررة للمستوى 2 تهدد السلامة أو بيئة التعلم. أمثلة: تكرار مخالفات المستوى 2، اللغة البذيئة، العراك، إحضار أشياء خطيرة، إتلاف الممتلكات عمدًا، التغيب عن المدرسة. العواقب: اجتماع أهل-طالب مع الإدارة، عقد سلوك، احتجاز، أو إيقاف.

Level 4 — Severe Consequences & Reviewደረጃ 4 — አስቸኳይ እርምጃ የሚሹ እጅግ ከባድ ጥፋቶችالمستوى 4 — العواقب الوخيمة والمراجعة

Grave offenses warranting immediate and significant action. Examples: repetition of a Level 3 offense, bringing a firearm, weapon, or explosive to school, harming or attempting to harm another person with a weapon, possessing, selling, or distributing controlled substances including cigarettes. Consequences: immediate suspension and review by the School Committee and Principal, which may lead to long-term suspension or expulsion.አስቸኳይና ከባድ እርምጃ የሚሹ እጅግ አደገኛ የሆኑ ጥፋቶች። ምሳሌዎች፦ የደረጃ 3 ጥፋትን መድገም፣ የጦር መሣሪያ፣ ስለታም ነገር ወይም ፈንጂ ይዞ መምጣት፣ በሌላ ሰው ላይ በመሣሪያ ጉዳት ማድረስ ወይም ለመጉዳት መሞከር፣ ሱስ አምጪ ንጥረ ነገሮችን (ሲጋራን ጨምሮ) መያዝ፣ መሸጥ ወይም ማሰራጨት። የሚወሰዱ እርምጃዎች፦ አስቸኳይ ከትምህርት ገበታ ማገድ እና ጉዳዩ ለተጨማሪ እርምጃ በትምህርት ቤቱ ኮሚቴና በርዕሰ መምህሩ እንዲገመገም ማድረግ፤ ይህም የረጅም ጊዜ እግድ ወይም ከትምህርት ቤት ሙሉ በሙሉ ማሰናበትን ሊያስከትል ይችላል።جرائم خطيرة تستدفع إجراء فوري وجدي. أمثلة: تكرار انتهاك المستوى 3، إحضار سلاح ناري أو متفجرات إلى المدرسة، إلحاق الأذى أو محاولة إلحاق الأذى بآخر بواسطة سلاح، حيازة أو بيع أو توزيع مواد خاضعة للرقابة بما في ذلك السجائر. العواقب: الإيقاف الفوري ومراجعة لجنة المدرسة والمدير، قد تؤدي إلى إيقاف طويل الأمد أو الفصل.

Understanding Bullying: Zero-Tolerance Policyጉልበተኝነትን መረዳት እና ምላሽ አሰጣጥفهم التنمر: سياسة عدم التسامح

Abadir School is committed to a safe, inclusive, and supportive environment free from bullying. Bullying is defined as repeated, intentional, hurtful behavior where there's a real or perceived imbalance of power between the aggressor and victim. We respond immediately: staff stop bullying at once, conduct a thorough investigation, inform parents of all parties, support victims, and apply progressive consequences according to the Behaviour Policy.አባዲር ትምህርት ቤት ከጉልበተኝነት የጸዳ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ሁሉን አቀፍ እና ደጋፊ የሆነ የመማሪያ አካባቢን ለመፍጠር ቁርጠኛ ነው። ጉልበተኝነት የምንገልጸው በተደጋጋሚ ሆን ተብሎ የሚፈጸም፣ ጎጂ የሆነና በጉልበተኛውና በተጎጂው መካከል እውነተኛ ወይም የታሰበ የሃይል አለመመጣጠን ያለበት ባህሪ እንደሆነ ነው። ምላሻችን ወዲያውኑ ይሰጣል፦ የትምህርት ቤቱ ሰራተኞች የጉልበተኝነት ድርጊት ሲመለከቱ ወዲያውኑ ያስቆማሉ፣ ጥልቅ ምርመራ ያደርጋሉ፣ የሚመለከታቸው አካላት ወላጆች በፍጥነት እንዲያውቁ ያደርጋሉ፣ ለተጎጂዎች ድጋፍ ይሰጣሉ፣ እና በሥነ-ምግባር ፖሊሲው መሠረት እየከበደ የሚሄድ እርምጃ ይወሰዳል።ت committed إلى توفير بيئة آمنة وشاملة وداعمة خالية من التنمر. نحدد التنمر على أنه سلوك متكرر ومتعمد ومؤذٍ حيث يوجد عدم توازن في القوة بين المعتدي والضحية. نرد فورًا: يوقف الموظفون التنمر فورًا، ويجري تحقيقًا شاملًا، ويُبلّغ أهالي جميع الأطراف، ويدعمون الضحايا، ويطبقون عواقب تتصاعد وفقًا لسياسة السلوك.

Forms of bullying include physical, verbal, social/relational, cyberbullying, and emotional bullying. We encourage students to report any bullying they experience or witness to a trusted adult.የጉልበተኝነት ዓይነቶች፦ አካላዊ ጥቃት፣ የቃል ጥቃት፣ ማኅበራዊ ጥቃት፣ የበይነመረብ (ሳይበር) ጥቃት እና ሥነ-ልቦናዊ ጥቃት። ማንኛውም ተማሪ ጉልበተኝነትን ሲመለከት ወይም ሲደርስበት ለሚያምነው የትምህርት ቤቱ አካል የማሳወቅ ኃላፊነት አለበት።تشمل أشكال التنمر الجسدي واللفظي والاجتماعي/العلائقي والإلكتروني والعاطفي. نحث الطلاب على الإبلاغ عن أي تنمر يعانونه أو يشاهدونه لشخص بالغ يثقون به.

Uniform, Dress Code & Appearanceየትምህርት ቤቱ የደንብ ልብስ፣ የአለባበስ ሥርዓትና የግል ገጽታ መመሪያالزي المدرسي وقواعد اللباس والمظهر

The uniform fosters identity, pride, equality, and security. It must be clean, neat, and in good repair. Please label each item with your child's name.የደንብ ልብሱ የማንነት፣ የኩራትና የባለቤትነት ስሜትን ለማዳበር፣ በተማሪዎች መካከል እኩልነትን ለማበረታታት፣ ከአለባበስ ምርጫ ጋር የተያያዙ ትኩረትን የሚከፋፍሉ ነገሮችን ለማስወገድ እና የትምህርት ቤቱን ደኅንነት ለማጠናከር ያገልግላል። ንጹህ፣ የተስተካከለና ያልተበላሽ መሆን አለበት። በእያንዳንዱ እቃ ላይ የልጅዎን ስም ያስቀምጡ።يعزز الزي المدرسي الهوية والفخر والمساواة والأمن. يجب أن يكون نظيفًا ومرتبًا وسليمًا. يرجى كتابة اسم الطفل على كل قطعة.

  • Trousers / Skirt: Gray for Secondary; Dark Blue / Blue-black for Primary Grades 5–8; Red for KG and Primary Grades 1–4.ሱሪ / ቀሚስ: ግራጫ ለሁለተኛ ደረጃ፣ ደማቅ ሰማያዊ / ሰማያዊ-ጥቁር ለአንደኛ ደረጃ ከ5ኛ እስከ 8ኛ፣ ቀይ ለKG እና ለአንደኛ ደረጃ ከ1ኛ እስከ 4ኛ።البنطلون/التنورة: رمادي للثانوي، أزرق داكن/أسود-أزرق للابتدائي 5–8، أحمر للروضة والابتدائي 1–4.
  • Shirt: White collared for Secondary & KG; Blue collared for Primary.ሸሚዝ: ነጭ ኮሌታ ለሁለተኛ ደረጃ እና KG፣ ሰማያዊ ኮሌታ ለአንደኛ ደረጃ።القميص: أبيض بياقة للثانوي والروضة، أزرق بياقة للابتدائي.
  • Sweater / Jumper: Black for Secondary; Dark Blue / Blue-black for Primary.ሹራብ: ጥቁር ለሁለተኛ ደረጃ፣ ደማቅ ሰማያዊ / ሰማያዊ-ጥቁር ለአንደኛ ደረጃ።السترة/السويتر: سوداء للثانوي، أزرق داكن/أسود-أزرق للابتدائي.
  • Hijab: Only white or black allowed. Hoodies are not allowed on the school compound.ሂጃብ፣ ነጭ ወይም ጥቁር ብቻ ነው የተፈቀደው። ኩኩል ያላቸው ሹራቦች በትምህርት ቤቱ ግቢ ውስጥ አይፈቀዱም።الحجاب: أبيض أو أسود فقط. لا يُسمح بالسترات ذات القبعة داخل المدرسة.
  • Appearance: No jeans, no caps indoors, no slippers or high heels, no tight/revealing clothing, no inappropriate images/messages. No make-up or nail polish. Only small stud earrings for girls; no jewelry for boys.የግል ገጽታ፣ ጂንስ አይፈቀድም፣ በት/ቤት ውስጥ ኮፍያ አይፈቀድም፣ ሸበጥ ወይም ረጅም ተረከዝ ያላቸው ጫማዎች አይፈቀዱም፣ ጠባብ/ገላን የሚያሳይ ልብስ አይፈቀድም። ሜካፕም ሆነ የጥፍር ቀለም አይፈቀድም። ለሴቶች ትናንሽ የጉትቻ ፍሬዎች ብቻ፣ ለወንዶች ጌጣጌጥ አይፈቀድም።المظهر: لا جينز، لا قبعات داخل المبنى، لا نعال أو كعوب عالية، لا ملابس ضيقة/فاضحة، لا صور أو رسائل غير لائقة. لا مكياج أو طلاء أظافر. فقط حلقات صغيرة للبنات؛ لا مجوهرات للأولاد.

Consequences for uniform violations: First violation — written warning; Second violation — parents contacted by telephone; Third violation — parents meet with the Principal and the student may not attend class without proper uniform.የደንብ ልብስ ደንብ ጥሰት ሲኖር የሚወሰዱ እርምጃዎች፦ የመጀመሪያ ጥፋት — የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ፣ ሁለተኛ ጥፋት — ወላጆች በስልክ ይደወላሉ፣ ሦስተኛ ጥፋት — ወላጆች ከርዕሰ መምህሩ ጋር ይገናኛሉ እና ተማሪው የትምህርት ቤቱን ደንብ ልብስ ካልለበሰ ወደ ክፍል አይገብም።عواقب مخالفات الزي: المخالفة الأولى — تحذير كتابي؛ المخالفة الثانية — الاتصال بالأهل هاتفيًا؛ المخالفة الثالثة — لقاء الأهل مع المدير وقد يُمنع الطالب من حضور الفصل بدون الزي المناسب.

Attendance & Punctualityየክትትል እና የሰዓት አክባሪነት መመሪያالحضور والانضباط

Regular attendance and punctuality are fundamental to academic success. Students must arrive by 7:50 AM for assembly and be in class by 8:00 AM. Late arrivals disrupt learning and will be addressed. If your child is absent, please inform the school office by 8:30 AM on the first day. A written note is required upon return; a medical certificate may be requested for absences over three consecutive days.የተማሪዎች መደበኛ የትምህርት ክትትልና ሰዓት አክባሪነት ለትምህርታዊ ውጤታማነታቸው ወሳኝ ነው። እያንዳንዱ ተማሪ ለጠዋት ሰልፍ ከጠዋቱ 1፡50 መድረስ እና 2፡00 ላይ በመማሪያ ክፍል ውስጥ መገኘት አለበት። ማርፈድ የክፍሉን የመማሪያ ማስተማር ሂደት ያደናቅፋል። ተማሪ ሲቀር፣ ወላጅ በዚያው ቀን ከጠዋቱ 2፡30 በፊት በስልክ ማሳወቅ አለበት። ሲመለስ ከወላጅ የተጻፈ ማብራሪያ ያስፈልጋል፤ ከ3 ቀናት በላይ ለሆነ ቀሪነት የህክምና ወረቀት ያስፈልጋል።الحضور المنتظم والانضباط أساسيان للنجاح الأكاديمي. يجب أن يصل الطلاب في 7:50 صباحًا للتجمع ويكونوا في الفصل بحلول 8:00 صباحًا. التأخر يؤثر على التعلم. إذا كان طفلكم غائبًا، يرجى إبلاغ مكتب المدرسة بحلول 8:30 صباحًا في اليوم الأول. مطلوب مذكرة كتابية عند العودة؛ وقد يُطلب شهادة طبية للغياب أكثر من ثلاثة أيام متتالية.

  • There is a 10-day limit for excused absences per trimester.በምክንያት የሚፈቀደው 10 ቀናት በአንድ መንፈቀ ብቻ ነው።حد الغيابات المبررة هو 10 أيام في كل فصل ثلاثي.
  • Planned absences require a "Leave Request Form" submitted at least one week in advance.የታቀደ ቀሪነት ቢያንስ 1 ሳምንት ቀደም ብሎ "የመልቀቂያ ቅጽ" መሞላትና መፈቀድ አለበት።الغيابات المخطط لها تتطلب استمارة طلب إجازة تُقدم قبل أسبوع على الأقل.
  • Absences over one week require two weeks' advance approval from administration.ከአንድ ሳምንት በላይ ለመቅረት የ2 ሳምንት ቅድመ-ይሁንታ ያስፈልጋል።الغياب لأكثر من أسبوع يتطلب موافقة إدارية مسبقة بأسبوعين.
  • Unexplained absences are considered truancy and may lead to disciplinary action.ያለማሳወቅ መቅረት እንደ ከባድ ጥፋት ይቆጠራል።الغياب بدون تفسير يُعتبر تغيبًا غير مبرر وقد يؤدي إلى إجراءات تأديبية.
  • Persistent absenteeism may result in withdrawal of tuition discounts or grade repetition.ተደጋጋሚ ቀሪነት የትምህርት ክፍያ ቅናሽ ያስሰርዛል፤ በከፋ ሁኔታም ክፍል መድገምን ያስከትላል።الغياب المتكرر قد يؤدي إلى سحب خصومات الرسوم أو إعادة الصف.

Electronics, Parties & Dating Policyየኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎችን፣ የልደት ድግሶችን እና የፍቅር ግንኙነት መመሪያالإلكترونيات والحفلات والعلاقات

Electronics: Mobile phones, tablets, laptops, and smartwatches are generally not permitted at school. Exceptions require explicit, prior permission from a teacher or school leadership for specific educational purposes. The school is not responsible for damage, loss, or theft of electronic devices brought to school.የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎች፣ እንደ ሞባይል ስልኮች፣ ታብሌቶች፣ ላፕቶፖች እና ስማርት ሰዓቶች ያሉ የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎች በአጠቃላይ በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ እንዲገቡ አይፈቀድላቸውም። ለተወሰኑ የትምህርት ዓላማዎች ከአስተማሪ ወይም ከትምህርት ቤቱ አመራር ግልጽና የቅድሚያ ፈቃድ ሲገኝ ብቻ ነው። በሚመጡ መሣሪያዎች ላይ ለሚደርስ ማንኛውም ጉዳት፣ መጥፋት ወይም ስርቆት አባዲር ትምህርት ቤት ኃላፊነት አይወስድም።الإلكترونيات: الهواتف المحمولة والأجهزة اللوحية والحواسيب المحمولة والساعات الذكية غير مسموح بها في المدرسة عمومًا. الاستثناءات تتطلب إذنًا مسبقًا واضحًا من المعلم أو الإدارة لأغراض تعليمية محددة. المدرسة غير مسؤولة عن تلف أو فقد أو سرقة الأجهزة.

Birthday & Class Parties: Birthday parties are not permitted during or after school hours on school premises. You may send biscuits to be shared with the class; please do not send sweets, cake, or drinks. Teachers may organize occasional class parties and will provide specific guidance.የልደት እና የክፍል ድግሶች፣ በአባዲር ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ በትምህርት ሰዓትም ሆነ ከትምህርት ሰዓት በኋላ የልደት ድግሶችን ማክበር አይፈቀድም። ልጅዎ የልደት ቀኑን ከክፍል ጓደኞቹ ጋር እንዲያከብር ከፈለጉ ለክፍሉ የሚሆን ብስኩት መላክ ይችላሉ፤ እባክዎ ከረሜላ፣ ኬክ ወይም መጠጦችን ከመላክ ይቆጠቡ። መምህራን አንዳንድ ጊዜ የክፍል ውስጥ ዝግጅቶችን ሊያዘጋጁ ይችላሉ።حفلات الأعياد والفصول: لا يُسمح بحفلات أعياد الميلاد خلال أو بعد ساعات المدرسة داخل المدرسة. يمكن إرسال بسكويت لمشاركته مع الفصل؛ يرجى عدم إرسال الحلويات أو الكعك أو المشروبات. قد ينظم المعلمون حفلات فصلية مناسبة ويقدمون توجيهات محددة.

Dating & PDA: Any dating or public display of affection is strictly forbidden on school premises and at school-sponsored activities. PDA includes physical contact such as hand holding, fondling, cuddling, and kissing. This behavior may lead to the highest form of disciplinary action.የተቃራኒ ፆታ ግንኙነት፣ በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥም ሆነ ትምህርት ቤቱ በሚያዘጋጃቸው ፕሮግራሞች ላይ ማንኛውም አይነት የፍቅር ግንኙነት እና ከሥርዓት ውጪ የሆኑ አካላዊ ንክኪዎች በጥብቅ የተከለከለ ነው። ከሥርዓት ውጪ የሆኑ ንክኪዎች ሲባልም እጅ መያያዝ፣ መተቃቀፍ፣ መሳሳም እና አላግባብ መነካካትን ይጨምራል። ይህንን ደንብ መተላለፍ ጥብቅ የሆነ የማስተካከያ እርምጃ ይወሰድበታል።المواعدة والتعبير العلني عن المشاعر: أي علاقة غرامية أو تعبير علني عن المشاعر ممنوع بشدة في أراضي المدرسة وأنشطتها الرسمية. يشمل ذلك التلامس الجسدي مثل الإمساك بالأيدي أو العناق أو التقبيل. قد يؤدي هذا السلوك إلى أشد العقوبات التأديبية.

Home-School Relationsበአባድር ትምህርት ቤት ስኬታማ ግንኙነትالعلاقة بين البيت والمدرسة

Communication, Visits & Grievancesግንኙነት፣ ጎብኚዎች እና የቅሬታ አቀራረብالتواصل والزيارات والشكاوى

Communication & Line of Communicationጥያቄ ወይም የሚያሳስብዎት ነገር ሲኖር መከተል ያለብዎት መንገድالتواصل وخطوط التواصل

We believe in open and effective communication between Abadir School and parents. If you have a question or concern, please follow these steps:በአባድር ትምህርት ቤት እና በወላጆች መካከል ግልጽና ውጤታማ የሆነ ግንኙነት እንዲኖር እናምናለን። በትምህርት ቤቱ ውስጥ የሚያጋጥምዎትን ማንኛውንም ጉዳይ በሥርዓት ለመፍታት እንዲረዳዎ የሚከተለውን መንገድ እንዲጠቀሙ በአክብሮት እንጠይቃለን፦نؤمن بالتواصل المفتوح والفعّال بين مدرسة أبادير والأهالي. إذا كان لديكم سؤال أو قلق، يرجى اتباع الخطوات التالية:

  1. Step 1የመጀመሪያ እርምጃالخطوة 1Speak with your child's teacher first.ጉዳዩን በቀጥታ ከሚመለከተው የልጅዎ መምህር ጋር ይወያዩ።تحدثوا مع معلم طفلكم أولاً.
  2. Step 2ሁለተኛ እርምጃالخطوة 2If unresolved, speak with the Principal overseeing your child's class.ችግሩ እልባት ካላገኘ የትምህርት ክፍሉን ኃላፊ (ርዕሰ መምህር) ያማክሩ።إذا لم يُحل، تحدثوا مع المدير المشرف على فصل طفلكم.
  3. Step 3ሦስተኛ እርምጃالخطوة 3For very serious matters, speak with a Director.ጉዳዩ በጣም ከባድና አስቸኳይ ከሆነ ከዳይሬክተሩ ጋር ቀጠሮ በመያዝ መወያየት ይችላሉ።للأمور الخطيرة جدًا، تحدثوا مع أحد المديرين.
  4. Step 4አራተኛ እርምጃالخطوة 4If still unresolved, contact a PTA representative for intervention, or formally request to present your concern to the PTA.ከእነዚህ ሁሉ ሂደቶች በኋላ አሁንም እርካታ ካላገኙ፣ የወላጅ-መምህራን ማኅበር (PTA) ተወካይ እንዲመለከተው ያድርጉ።إذا لم يُحل بعد، تواصلوا مع ممثل جمعية الآباء والمعلمين للتدخل، أو اطلبوا رسميًا عرض قلقكم على الجمعية.

Our main communication channels are email, SMS, and the official Telegram group. The school office is open Monday to Friday, 8:00 AM – 4:00 PM. Please update the school immediately if your phone, email, address, or emergency contacts change.የትምህርት ቤታችን ዋነኛ የመረጃ ማስተላለፊያ መንገዶች ኢሜይል፣ የጽሑፍ መልዕክት (SMS) እና የትምህርት ቤቱ ይፋዊ የቴሌግራም ግሩፕ ናቸው። የትምህርት ቤቱ ጽ/ቤት ከሰኞ እስከ ዓርብ ከጠዋቱ 2:00 እስከ ቀኑ 10:00 ሰዓት ድረስ ክፍት ነው። የመገናኛ አድራሻዎ (ስልክ፣ ኢሜይል፣ የመኖሪያ አድራሻ) ወይም የአስቸኳይ ጊዜ ተጠሪዎችዎ ሲቀየሩ በአስቸኳይ ማሳወቅ የእርስዎ ኃላፊነት ነው።قنوات التواصل الرئيسية لدينا هي البريد الإلكتروني والرسائل النصية والمجموعة الرسمية على Telegram. مكتب المدرسة مفتوح من الاثنين إلى الجمعة، من 8:00 صباحًا حتى 4:00 مساءً. يرجى إبلاغ المدرسة فورًا بتغيير رقم الهاتف أو البريد الإلكتروني أو العنوان أو جهات الاتصال في الطوارئ.

Visiting School, PTA & Fundraisingትምህርት ቤቱን መጎብኘት፣ የወላጅ-መምህራን ማኅበር እና የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅቶችزيارة المدرسة وجمعية الأهالى وجمع التبرعات

Visitors are welcome but must report to the Principal's office upon arrival. Classroom visits require advance scheduling; visitors must sit quietly and not disrupt lessons. Please do not bring additional children or adults to classroom visits without prior Principal approval.አባዲር ትምህርት ቤት ጎብኚዎችን በደስታ ይቀበላል፤ ሆኖም ለደህንነት ሲባል ሁሉም ጎብኚዎች እንደደረሱ ለትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ቢሮ ሪፖርት ማድረግ አለባቸው። የመማሪያ ክፍሎችን ለመጎብኘት በትምህርት ቤቱ ጽ/ቤት በኩል አስቀድመው ቀጠሮ ማስያዝ ያስፈልጋል። ጎብኚዎች በጸጥታ መቀመጥ እና የመማር ማስተማር ሂደቱን አለማወክ ይጠበቅባቸዋል። ያለ ርዕሰ መምህሩ ቅድመ ፈቃድ ተጨማሪ ልጆችንም ሆነ ሌሎች አዋቂዎችን ወደ ክፍል ይዞ መምጣት የተከለከለ ነው።الزوار مرحب بهم، لكن يجب عليهم التوجه إلى مكتب المدير عند الوصول. تتطلب زيارات الفصول جدولة مسبقة؛ على الزوار الجلوس بهدوء وعدم إزعاج الدروس. يرجى عدم إحضار أطفال إضافيين أو بالغين إلى زيارات الفصول دون موافقة المدير المسبقة.

The Parent-Teacher Association (PTA) is a key part of our community, fostering collaboration, supporting school programs, organizing events, and providing a forum for parent input. All parents are encouraged to join. Fundraising activities must be approved by the school administration and align with school values and goals.የወላጅ-መምህራን ማኅበር (PTA) የትምህርት ቤታችን ማኅበረሰብ ዋነኛ አካል ነው። በትምህርት ቤቱ እና በወላጆች መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር፣ የትምህርት ቤቱን ፕሮግራሞች መደገፍ፣ የተለያዩ ዝግጅቶችን ማዘጋጀት እና የወላጆችን ሀሳብና አስተያየት የሚያቀርቡበት መድረክ መፍጠር ናቸው። ሁሉም ወላጆች የማኅበሩ አባል በመሆን በንቃት እንዲሳተፉ ይበረታታሉ። ሁሉም የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅቶች በትምህርት ቤቱ አስተዳደር መጽደቅ እና መፈቀድ አለባቸው።جمعية الآباء والمعلمين (PTA) جزء أساسي من مجتمعنا، تعزز التعاون، تدعم برامج المدرسة، تنظم الفعاليات، وتقدم منبرًا لآراء الأهالي. نشجع جميع الأهالي على الانضمام. يجب أن تحظى أنشطة جمع التبرعات بموافقة الإدارة وأن تتماشى مع قيم وأهداف المدرسة.

Grievance Procedureየቅሬታ አቀራረብ ሥነ-ሥርዓትإجراء تقديم الشكاوى

We strive for a respectful environment. If a concern arises, first discuss it directly with the involved party (e.g., teacher, administrator) for an amicable resolution. If unresolved, schedule an appointment with the Principal. Should the matter still not be resolved, submit a detailed written grievance to the School Committee, who may investigate or involve the School Board. For final resolution, the School Arbitration Committee will be consulted to make a conclusive decision.ትምህርት ቤታችን በአክብሮት ላይ የተመሠረተ የመማር ማስተማር ከባቢ ለመፍጠር ይተጋል። ማንኛውም ቅሬታ ወይም ሥጋት ሲፈጠር፣ ችግሩ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ በመጀመሪያ ጉዳዩ ከሚመለከተው አካል ጋር በቀጥታ በመወያየት እንዲፈታ ይበረታታል። በዚህ መንገድ መፍትሄ ካልተገኘ፣ ከርዕሰ መምህሩ ጋር ቀጠሮ ይዞ መወያየት ይቻላል። ጉዳዩ አሁንም እልባት ካላገኘ፣ ዝርዝር ቅሬታውን በጽሑፍ ለትምህርት ቤቱ ኮሚቴ ማቅረብ ይቻላል። ለመጨረሻ ውሳኔ ጉዳዩ ለትምህርት ቤቱ የግልግል ኮሚቴ ቀርቦ አግባብነት ያለው ውሳኔ እንዲሰጥ ይደረጋል።نسعى جاهدين لبيئة محترمة. إذا نشأ قلق، ناقشوه أولاً مباشرة مع الطرف المعني (مثل المعلم أو الإداري) لحل ودي. إذا لم يُحل، حددوا موعدًا مع المدير. إذا استمر الأمر دون حل، قدموا شكوى مكتوبة مفصلة للجنة المدرسة، التي قد تُحقق أو تُحيل الأمر لمجلس المدرسة. للحل النهائي، تُستشهر لجنة التحكيم المدرسية لتتخذ قرارًا نهائيًا.

Roles & Responsibilities of Parentsየወላጆች ሚና እና ኃላፊነትأدوار ومسؤوليات الأهالي

  • Communicate respectfully with staff and other parents; address concerns directly with the school starting with the teacher.ከመምህራን፣ ከአስተዳደር ሰራተኞች እና ከሌሎች ወላጆች ጋር የሚደረግ ግንኙነት ሁልጊዜ በአክብሮት ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት። ማንኛውንም ቅሬታ ከአስተማሪው በመጀመር ለትምህርት ቤቱ ማቅረብ ይገባል።التواصل باحترام مع الموظفين والأهالي الآخرين؛ عرض القلق مباشرة مع المدرسة بدءًا من المعلم.
  • Ensure your child attends school on time and regularly; report absences promptly. Support learning at home (homework, reading, study).ልጅዎ በየቀኑ በሰዓቱ ትምህርት ቤት መገኘቱን ማረጋገጥ እና ሲቀር በወቅቱ ማሳወቅ። ልጅዎ የቤት ስራውን እንዲሰራ፣ እንዲያነብ እና ለትምህርቱ እንዲዘጋጅ በቤት ውስጥ ድጋፍ ማድረግ።ضمان حضور طفلكم في الوقت المحدد وبانتظام؛ إبلاغ الغياب فورًا. دعم التعلم في المنزل (الواجبات، القراءة، الدراسة).
  • Dress appropriately when visiting. Do not disrupt classes or school operations. Smoking, inappropriate language, and aggressive behavior are prohibited.ትምህርት ቤቱን በሚጎበኙበት ጊዜ አግባብነት ያለው አለባበስ መልበስ። የመማር ማስተማር ሂደቱን ወይም የትምህርት ቤቱን ስራ ማወክ አይፈቀድም። ማጨስ፣ ተገቢ ያልሆኑ ቃላትን መጠቀም እና ጠበኛ ባህሪ ማሳየት ክልክል ነው።اللباس المناسب عند الزيارة. عدم إزعاج الفصول أو عمل المدرسة. يُمنع التدخين واللغة غير اللائقة والسلوك العدواني.
  • Inform the school of any health issues, allergies, or special needs. Keep sick children home. Drop off and pick up students on time.ልጅዎን የሚመለከት ማንኛውንም የጤና ችግር፣ አለርጂ ወይም ልዩ ፍላጎት ለትምህርት ቤቱ ማሳወቅ። የህመም ስርጭትን ለመከላከል የታመመ ልጅን ቤት ውስጥ ማቆየት። ተማሪዎችን በሰዓቱ ትምህርት ቤት ማድረስና መውሰድ።إبلاغ المدرسة بأي مشاكل صحية أو حساسية أو احتياجات خاصة. إبقاء الأطفال المرضى في المنزل. إيصال واستلام الطلاب في الوقت المحدد.
  • Pay school fees on time. Make donations through official school channels only.የትምህርት ቤት ክፍያዎችን በወቅቱ መፈጸም። ማንኛውንም ድጋፍ ወይም ልገሳ በኦፊሴላዊው የትምህርት ቤቱ መስመር ብቻ መፈጸም።دفع الرسوم الدراسية في الوقت المحدد. التبرع عبر القنوات الرسمية للمدرسة فقط.
  • Read and follow all school policies (academic, discipline, ethics). Do not record or take photos on school grounds without permission.ሁሉንም የትምህርት ቤቱን ፖሊሲዎች (የትምህርት፣ የዲሲፕሊን፣ የስነምግባር) አንብቦ መረዳትና መከተል። ያለፈቃድ በትምህርት ቤቱ ግቢ ውስጥ ፎቶ ማንሳትም ሆነ ቪዲዮ መቅረጽ አይፈቀድም።قراءة واتباع جميع سياسات المدرسة (الأكاديمية، الانضباط، الأخلاق). عدم التصوير أو تسجيل الفيديو داخل المدرسة بدون إذن.
Administrative & Financial Mattersአስተዳደራዊና ፋይናንስ ነክ ጉዳዮችالشؤون الإدارية والمالية

Admissions, Fees & Facilitiesቅበላ፣ ክፍያዎች እና ጋራ ንብረትالقبول والرسوم والمرافق

Admissions & Registration Proceduresየተማሪዎች ቅበላና ምዝገባإجراءات القبول والتسجيل

Re-enrollment for current students: The registration period for returning students is from July 21, 2025, to August 1, 2025. Students with uncleared tuition or on final disciplinary warnings may be denied re-enrollment.ለነባር ተማሪዎች ዳግም ምዝገባ፣ ሙሉ ምዝገባ ከ ሐምሌ 14፣ እስከ ሐምሌ 25 ድረስ መጠናቀቅ አለበት። የትምህርት ክፍያ ያላጠናቀቁ ወይም ከባድ የሥነ-ምግባር ማስጠንቀቂያ ያላቸው ተማሪዎች ዳግም ላይመዘገቡ ይችላሉ።إعادة التسجيل للطلاب الحاليين: فترة التسجيل للطلاب العائدين من 21 يوليو إلى 1 أغسطس 2025. قد يُرفض تسجيل الطلاب الذين لم يسددوا الرسوم أو الموجودين تحت تحذيرات تأديبية نهائية.

Open registration: For remaining spaces, open registration begins August 1, 2025, for both returning and new students on a first-come, first-served basis, with priority given to families who already have a child enrolled at Abadir School. Siblings of existing students receive priority from August 2–13, 2025.ክፍት ምዝገባ፣ ለቀሪ ቦታዎች ክፍት ምዝገባ ከነሐሴ 1 ጀምሮ ለነባርም ሆነ ለአዲስ ተማሪዎች ይጀምራል። በአባዲር ትምህርት ቤት ቀደም ሲል ልጅ ያላቸው ቤተሰቦች ቅድሚያ ያገኛሉ። አባዲር ትምህርት ቤት ውስጥ እህት ወይም ወንድም ያላቸው ልጆች ከ ሐምሌ 26 እስከ ነሐሴ 6 ቅድሚያ የማግኘት እድል አላቸው።التسجيل المفتوح: للمقاعد المتبقية، يبدأ التسجيل المفتوح في 1 أغسطس 2025 للطلاب العائدين والجدد على أساس من يأتي أولاً يُخدم أولاً، مع أولوية للعائلات التي لديها طفل مسجل في أبادير. يحصل الإخوة على أولوية من 2 إلى 13 أغسطس 2025.

New student application: Submit the Enrollment Application Form, Family Information Form, Tuition Contract, Tuition Policy Provisional Agreement Form, birth certificate, Fayda ID, and academic transcripts (including conduct records) to the Record Office. Applicants may undergo a written test or interview. Assessments are scheduled only after all required documentation is submitted.ለአዲስ ተማሪዎች የማመልከቻ ሂደት፣ የምዝገባ ማመልከቻ ቅጽ፣ የቤተሰብ መረጃ ቅጽ፣ የትምህርት ክፍያ ውል፣ የትምህርት ክፍያ ፖሊሲ ጊዜያዊ ስምምነት ቅጽ፣ የልደት የምስክር ወረቀት፣ የፈይዳ መታወቂያ እና የትምህርት ማስረጃዎች (የሥነ-ምግባር ሪፖርትን ጨምሮ) ለሰነድ ክፍል ያስገቡ። አመልካቾች ስለ ተማሪውና ቤተሰቡ የበለጠ ለማወቅ የሚረዳ የጽሑፍ ፈተና ወይም ቃለ-መጠይቅ ሊደረግላቸው ይችላል። ምዘናዎች የሚካሄዱት ሁሉም አስፈላጊ ሰነዶች ከገባ በኋላ ብቻ ነው።طلب الطالب الجديد: قدموا استمارة الطلب، واستمارة معلومات العائلة، وعقد الرسوم، واستمارة اتفاق سياسة الرسوم المؤقتة، وشهادة الميلاد، وبطاقة فايدا، والسجلات الأكاديمية (بما في ذلك سجلات السلوك) إلى مكتب السجلات. قد يخضع المتقدمون لاختبار كتابي أو مقابلة. يتم جدولة التقييمات فقط بعد تقديم جميع المستندات المطلوبة.

Tuition Fees & Payment Schedulesየትምህርት ክፍያና የአከፋፈል መረጃالرسوم الدراسية وجداول الدفع

Abadir School strives to make quality education accessible. All tuition and fee payments must be made exclusively through Zemzem Schoolpay. A 1,000 ETB penalty applies to each payment made through any other method without prior school approval.አባዲር ትምህርት ቤት ጥራት ያለው ትምህርትን ተደራሽ ለማድረግ ይጥራል። ሁሉም የትምህርት እና ሌሎች ተያያዥ ክፍያዎች መፈጸም ያለባቸው በዘምዘም ስኩልፔይ (Zemzem Schoolpay) በኩል ብቻ ነው። ከትምህርት ቤቱ ቅድመ ፈቃድ ሳያገኙ ከተፈቀደው የዘምዘም ስኩልፔይ ሥርዓት ውጪ በሌላ መንገድ ለሚፈጽሙት እያንዳንዱ ክፍያ የ1,000 ብር ቅጣት ይተገበራል።تسعى مدرسة أبادير إلى جعل التعليم الجيد في متناول الجميع. يجب دفع جميع الرسوم الدراسية والرسوم الأخرى حصريًا عبر Zemzem Schoolpay. يُطبق غرامة 1000 بير على كل دفع يتم عبر أي طريقة أخرى بدون موافقة مسبقة من المدرسة.

LevelደረጃالمستوىMonthly (ETB)ወርሃዊ (ብር)شهريًا (بير)Quarterly (ETB)የሩብ ዓመት (ብር)ربع سنوي (بير)Registration (ETB)የምዝገባ (ብር)التسجيل (بير)
KG 14,35013,0501,087.50
KG 2 & 33,1909,570797.50
Primary 1–6አንደኛ ደረጃ 1–6الابتدائي 1–62,4507,350612.50
Primary 7–8አንደኛ ደረጃ 7–8الابتدائي 7–82,5377,611634.25
Secondaryሁለተኛ ደረጃالثانوي2,9458,835736.25

Payment Plansየክፍያ እቅድ አማራጮችخطط الدفع

PlanአማራጭالخطةDetailsዝርዝርالتفاصيلDue Datesየመክፈያ ቀኖችمواعيد الاستحقاق
Plan Aአማራጭ ሀالخطة أOne-time full year paymentየአንድ ጊዜ ሙሉ የትምህርት ዓመት ክፍያدفع مرة واحدة للعام كاملSeptember 30, 2025መስከረም 19 – 30, 201830 سبتمبر 2025
Plan Bአማራጭ ለالخطة بQuarterly paymentsየሩብ ዓመት ክፍያدفعات ربع سنويةOct 11, 2025; Jan 9, 2026; Apr 9, 2026ጥቅምት 1, ታህሳስ 1, መጋቢት 1, 201811 أكتوبر 2025؛ 9 يناير 2026؛ 9 أبريل 2026
Plan Cአማራጭ ሐالخطة جMonthly paymentsየወርሃዊ ክፍያدفعات شهريةBetween 25th–30th of each Ethiopian monthበየወሩ ከ25ኛው እስከ 30ኛው ቀንبين 25 و30 من كل شهر إثيوبي

Late Payment Penaltiesክፍያ ሲዘገይ ስለሚወሰዱ እርምጃዎችعقوبات التأخير في الدفع

A progressive late fee is charged for payments not received by the due date. For quarterly plans, penalty increases from 10% to 15% to 20% of outstanding tuition, and after the final deadline the student becomes ineligible to attend class. For monthly plans, a 25% penalty is applied immediately, plus an additional 15% for every subsequent 5-day period. Students with overdue payments for more than two consecutive terms will be ineligible to attend class. A student will be suspended after three instances of late payment, regardless of whether they occur in consecutive terms.ክፍያ በተቀመጠለት ጊዜ ውስጥ ሳይፈጸም ሲቀር እንደዘገየበት ጊዜ መጠን ቅጣቱ ከ10% እስከ 20% ያድጋል። ለወርሃዊ እቅድ፣ ክፍያው በጊዜው ካልተከፈለ ወዲያውኑ 25% ቅጣት ይተገበራል፤ ከዚያ በኋላ ለእያንዳንዱ ተከታይ የአምስት ቀናት ጊዜ ተጨማሪ 15% ቅጣት ይጨመራል። ለተከታታይ ሁለት የክፍያ ጊዜያት ክፍያ ያላጠናቀቁ ተማሪዎች ከክፍል ገበታ ይታገዳሉ። በድምሩ ለሶስተኛ ጊዜ ክፍያ ያዘገየ ተማሪ ከትምህርት ገበታ ይታገዳል።تُفرض رسوم تأخير تصاعدية للدفعات غير المستلمة في الموعد. للخطط الربع السنوية، تزداد الغرامة من 10% إلى 15% إلى 20% من الرسوم المتأخرة، وبعد الموعد النهائي لا يحق للطالب حضور الفصل. للخطط الشهرية، تُطبق غرامة 25% فورًا، زائد 15% إضافية لكل فترة 5 أيام لاحقة. الطلاب المتأخرون في الدفع لأكثر من فترتين متتاليتين يُمنعون من حضور الفصل. يُوقف الطالب بعد ثلاث حالات تأخر في الدفع.

Withdrawal & Delinquent Accountsየትምህርት ማቋረጥ ሥርዓትና የዘገዩ ክፍያዎችالانسحاب والحسابات المتأخرة

All withdrawal requests must be submitted in writing to the school office. A student who withdraws cannot re-enroll within the same academic year and must reapply as a new candidate. Tuition liability upon withdrawal depends on the withdrawal date: 25% if between October–December 2025; 50% if between January–March 2026; 100% if after April 2026. An account is considered delinquent if payment is not received within 30 days of the due date; students with delinquent accounts will not be admitted to class until the balance is settled or a formal payment plan is agreed upon. If you anticipate financial difficulties, inform the school in writing immediately.ማንኛውም ተማሪ ትምህርቱን ለማቋረጥ ከፈለገ ጥያቄውን በጽሑፍ ለትምህርት ቤቱ ጽ/ቤት ማቅረብ ይኖርበታል። አንድ ጊዜ ትምህርቱን ያቋረጠ ተማሪ በዚያው የትምህርት ዘመን ውስጥ ተመልሶ ዳግም መመዝገብ አይችልም። ተማሪው ከጥቅምት እስከ ታኅሣሥ 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ ትምህርቱን ካቋረጠ 25%፣ ከጥር እስከ መጋቢት 2018 50%፣ ከሚያዝያ 2018 በኋላ 100% የክፍያ ግዴታ አለበት። አንድ የክፍያ ሂሳብ ከነበረበት ቀን አንስቶ በ30 ቀናት ውስጥ ሳይከፈል ከቀረ እንደ ውዝፍ ሂሳብ ይቆጠራል። ተደጋጋሚ የውዝፍ ሂሳብ ታሪክ ያለው ተማሪ በቀጣይ የትምህርት ዘመናት ከዳግም ምዝገባ ብቁ እንዳይሆን ሊያደርገው ይችላል። የገንዘብ ችግር እንደሚያጋጥምዎት አስቀድመው ካሰቡ ይህንኑ ወዲያውኑ ለትምህርት ቤቱ በጽሑፍ ማሳወቅ ይኖርብዎታል።يجب تقديم جميع طلبات الانسحاب كتابيًا إلى مكتب المدرسة. لا يمكن للطالب الذي ينسحب إعادة التسجيل في نفس العام الدراسي ويجب إعادة التقديم كطالب جديد. تبعية الرسوم الدراسية تعتمد على تاريخ الانسحاب: 25% بين أكتوبر–ديسمبر 2025؛ 50% بين يناير–مارس 2026؛ 100% بعد أبريل 2026. يُعتبر الحساب متأخرًا إذا لم يُستلم الدفع خلال 30 يومًا من تاريخ الاستحقاق؛ ولا يُسمح للطلاب ذوي الحسابات المتأخرة بحضور الفصل حتى تسوية الرصيد أو الاتفاق على خطة دفع رسمية. إذا كنتم تتوقعون صعوبات مالية، أبلغوا المدرسة كتابيًا فورًا.

Use of School Facilities & Propertyየጋራ ንብረታችንን ስለመጠበቅاستخدام مرافق ومالية المدرسة

School facilities are primarily for the educational and co-curricular activities of Abadir students and staff during school hours. External groups must request use in writing to the Head of School. All students, parents, and visitors must treat school property with care and respect. Damage caused by negligence or malicious intent is the financial responsibility of the individual or family concerned. Unauthorized access outside school hours is strictly prohibited.የግቢያችን ዋነኛ አገልግሎት ለልጆቻችን የመማር ማስተማር ሂደትና ለተጨማሪ የክህሎት ማዳበሪያ እንቅስቃሴዎች ነው። ከትምህርት ቤቱ ማኅበረሰብ ውጪ ያሉ ወገኖች ግቢውን መጠቀም ከፈለጉ ጥያቄያቸውን ለትምህርት ቤቱ ኃላፊ በጽሑፍ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ሁሉም ተማሪዎች፣ ወላጆችና ጎብኚዎች የትምህርት ቤቱን ንብረትና መገልገያዎች በጥንቃቄና በአክብሮት መያዝ ይጠበቅባቸዋል። በቸልተኝነት ወይም ሆን ተብሎ በሚደረግ ድርጊት ለሚደርስ ማንኛውም ጉዳት፣ ግለሰቡ ወይም የሚመለከተው ቤተሰብ ለካሣ ክፍያ ኃላፊ ይሆናል። ከትምህርት ሰዓት ውጪ ወይም ያለቅድመ ፈቃድ ወደ ትምህርት ቤቱ ግቢ መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው።المرافق المدرسية مخصصة بشكل أساسي للأنشطة التعليمية واللامنهجية لطلاب وموظفي أبادير خلال ساعات المدرسة. يجب على الجماعات الخارجية طلب الاستخدام كتابيًا من مدير المدرسة. يجب على جميع الطلاب والأهالي والزوار التعامل مع ممتلكات المدرسة بعناية واحترام. يتحمل الفرد أو العائلة المسؤولية المالية عن الأضرار الناجمة عن الإهمال أو النية الخبيثة. يُمنع الدخول بدون إذن خارج ساعات المدرسة.

Parent Acknowledgementየወላጅ ስምምነትإقرار الأهالي

Acknowledgement of Receipt & Understandingየመመሪያውን መቀበልና መረዳት ስለማረጋገጥإقرار باستلام وفهم الدليل

I/We acknowledge that I/we have received, read, and thoroughly understood the Abadir School Parent–Student Handbook for the 2025–2026 academic year. I/We understand and agree to abide by all the policies, procedures, and expectations outlined within this handbook, including the ethical and behavioral guidelines for parents, students, and staff. I/We commit to supporting Abadir School in providing a positive, safe, and effective learning environment for my/our child(ren).ይህንን ቅጽ በመፈረም፣ ለ2017 የትምህርት ዘመን የተዘጋጀውን የአባዲር ትምህርት ቤት የወላጅ-ተማሪ መመሪያ መጽሐፍ እንደተቀበልኩ፣ እንዳነበብኩትና ይዘቱን በሚገባ እንደተረዳሁት አረጋግጣለሁ። በመመሪያው ውስጥ ያሉትን ደንቦችና ሥርዓቶች በሙሉ ለማክበር እንዲሁም ልጄ/ልጆቼ የተሻለ የመማሪያ አካባቢ እንዲኖራቸው ትምህርት ቤቱን ለመደገፍ ሙሉ ፈቃደኛ መሆኔን እገልጻለሁ።أقر/نقر بأنني/نحن تسلمنا وقرأنا وفهمنا بدقة دليل أبادير للأهالي والطلاب للعام الدراسي 2025–2026. أفهم/نفهم ونوافق على الالتزام بجميع السياسات والإجراءات والتوقعات الواردة في هذا الدليل، بما في ذلك الإرشادات الأخلاقية والسلوكية للأهالي والطلاب والموظفين. أتعهد/نتعهد بدعم مدرسة أبادير في توفير بيئة تعليمية إيجابية وآمنة وفعالة لطفلي/أطفالي.

I/We understand that this handbook is subject to review and revision, and I/we will be informed of any significant changes.መመሪያው በየጊዜው ሊሻሻል እንደሚችልና ለውጦች ሲኖሩ መረጃ እንደሚደርሰኝ ተረድቻለሁ።أفهم/نفهم أن هذا الدليل قابل للمراجعة والتعديل، وسيتم إبلاغي/نا بأي تغييرات جوهرية.

Parent/Guardian 1 Full Nameየወላጅ/አሳዳጊ 1 ስምاسم ولي الأمر/الوصي 1

Signatureፊርማالتوقيع

Parent/Guardian 2 Full Nameየወላጅ/አሳዳጊ 2 ስምاسم ولي الأمر/الوصي 2

Signatureፊርማالتوقيع

Dateቀንالتاريخ

Student's Full Name(s) and Grade Level(s)የተማሪ(ዎች) ስም እና ክፍልاسم الطالب/الطلاب والصف/الصفوف

Chat with Abadir School

We reply on Telegram

Choose a topic and send your message. We will reply on Telegram during office hours.

Powered by Telegram